Published On Apr 21, 2022
ባንካችን አለም አቀፉ የሴቶች ቀን ማርች 8 ጋር በተያያዘ ‘’እችላለሁ’’ በሚል መሪ ቃል ባከናወነው የግጥም እና የሙዚቃ ውድድር ላይ በየዘርፉ ከ1ኛ-3ኛ ለወጡት ተወዳዳሪዎች ሽልማትና የምስክር ወረቀት ሰጥቷል፡፡
በዚህ መርሃ ግብር የድምፅና የግጥም ተሰጥኦ ያላቸው እንስቶች እንዲወዳደሩ በማድረግ ከ 33 የድምፅ ተወዳዳሪዎችና ከ 318 የግጥም ተወዳዳሪዎች መካከል በዳኞችና በአድማጭ ተሳታፊዎች ከፍተኛ ድምፅ ያገኙትን ሶስት ሶስት አሸናፊዎች ተለይተው ለሽልማት በቅተዋል፡፡
በሥነስርዓቱም ለ1ኛ 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) 2ኛ 30,000.00(ሠላሳ ሺህ ብር) 3ኛ 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) ሽልማት የተበረከተ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ አሸናፊዎች ያሸነፉበትን የግጥም እና የሙዚቃ ስራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡
በሌላ በኩል የመርሃ-ግብሩ ሌላኛው አካል በነበረው የሥራ ፈጣዎችን የብድር ጥያቄ በማወዳደር ለአሸናፊዎቹ ከገበያው በአነሰ የወለድ ምጣኔና ካለመያዣ እስከ ብር 300,000.00 (ሦስት መቶ ሺህ) ድረስ ብድር መመቻቸቱ ተገልጿል፡፡
show more