Published On Sep 27, 2024
ከኦርቶዶክሱም ይልቅ የበዛው የፕሮቴስታንቱ ያለማወቅ ምንፍቅና ክፍል አራት ማጠቃለያ
ተሃድሶ ለሁለቱም ቤት የግድ ያሰፈልጋል :: በቀድሞው ቤታችን ጳጳሳት ካህናትና ምዕመናን መታደስ አለባቸው እንደምንል ሁሉ በፕሮቴስታንቱም እንዲሁ ፓስተሮች ነቢያትና አገልጋዮች የቃሉና የመንፈሱ ተሃድሶ የግድ ያስፈልጋቸዋል እንላለን :: ለምን ብለን ስንጠይቅ ደግም መጽሐፍቅዱሳችን ሙሉውን መልስ ይሰጠናል :: እንዲሁም ኢዩ በአልን ከእስራኤል አጠፋ ነገር ግን እስራኤልን ካሳተው ከናባጥ ልጅ ከኢዮርብአም ሃጢአት በቤቴልና በዳን ከነበሩት ከወርቁ እንቦሶች ኢዩ አልራቀም ይለናል ( 2ኛ ነገሥት 10 ፡ 28 - 31 ) የተጻፈልንን በጽኑ እናንብብ እንመልከት ጌታ ይርዳን ቊርጠኛ ለሆነው ለዚህ የተሃድሶ እውነትም ያዘጋጀን ለዚህም አሜን ወአሜን ለይኩን ለይኩን ነው የሚባለው ተባረኩ !!!!
show more